ኢትዮጵያ በጎረቤት ጅቡቲ በምትዋሰንበት የደንበር አካባቢ በርካታ ወታደሮችን ማስፈሯ ተገለጠ። ይኸው በኮሎኔል አመራር ስር የተሰማራው ወታደራዊ ሃይል ታዱራህ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በምትገኘው የባልሆ ከተማ የሰፈረ ሲሆን፣ የወታደሮቹ ቁጥር በትንሹ 150 እንደሚደርስ በደህንነት ዙሪያ ሪፖርቶችን የሚያቀርበው አፍሪካ ኢንተሊጀንስ አርብ ዘግቧል። በኢትዮጵያ በአፋር ክልል ያለው የጸጥታ ሁኔታ አለመረጋጋትን እያሳየ እንደመጣ ያወሳው የደህንነት ተቋሙ ወታደሮቹ መሰማራት በተጠርጣሪ ታጣቂዎች […]
