በወልቃይት የዐማራ ማንነት ጥያቄ አቅራቢ ኮሚቴዎች ላይ የሚደርሰውን አፈናና ግድያ እንዲቆም የሚጠይቅ ሰላማዊ ሰልፍ በጎንደር ከተማ እሁድ ሐምሌ 17 ቀን 2008 ዓ.ም. ለማካሔድ የአገር ሽማግሌዎችና የሕዝብ ተወካዮች ለከተማ አስተዳደሩ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ጥያቄ አቅራቢዎቹ እንደገለጹት አርብ ሐምሌ 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ከሰአት በኋላ አዎንታዊ መልስ እንደሚሰጣቸው ከከተማ አስተዳደሩ ተነግሯቸዋል፡፡ እሁድ ዐማሮች በሚያደርጉት ሰላማዊ ሰልፍ ከግማሽ ሚሊዮን […]
