በሰሜናዊ የፈረንሳይ ግዛት በምትገኘው ካላይስ የስደተኞች ጊዜያዊ መጠለያ ውስጥ በነበሩ ስደተኞች መካከል በተቀሰቀሰ ግጭት አንድ ኢትዮጵያዊ ደረቱ አካባቢ በጩቤ ተወግቶ ህይወቱ ማለፉን የዘገበው የድረ ገጽ ጋዜጣ የሆነው ላ ቮስ ደ ኖርድ ሌሎች ስድስት ስደተኞችም ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቋል፡፡ ጋዜጣው የካላይስ አካባቢን ፖሊሶች በመጥቀስ እንደዘገበው የ37 ዓመቱ ኢትዮጵያዊ ለሞት የተዳረገው ደረቱና ጀርባው ላይ በጩቤ በመወጋቱ ነው፡፡ […]
