መስፍን ወልደ ማርያም ኅዳር/2009 የአሜሪካንን ምርጫ ስከታተል ሃምሳ ዓመታት አልፈውኛል፤ ነገር ግን ተወዳዳሪ ፖሊቲከኞቹንም፣ ሕዝቡንም፣ ጋዜጠኞችንም በሚያሳፍር (የሚያፍር ከተገኘ!) ሁኔታ በጭቅጭቅና በስድብ የታጀበ ውድድር ስመለከት ይህ የመጀመሪያዬ ነው፤ እኛ ወደነሱ እንሄዳለን ስንል እነሱ ወደኛ እየመጡ ይመስላል፡፡ በመጀመሪያ በኢትዮጵያ ፖሊቲከኞቻችን ሁሉ ፖሊቲከኛ መሆን የሚቸገሩበትን ምክንያት በአሜሪካኑ የምርጫ ውድድር ላይ በገሀድ ያየነው ይመስለኛል፤ ኦባማና ትረምፕ በሃያ አራት […]
