ሰሞኑን ልጄ ሙሴን አሞብኝ ሀኪም ቤት እየተመላለስኩ ነው፡፡ የአራት አመቱ ልጄ ሙሴ ወንደሰን ይባላል፡፡ የስምንት ወር ልጅ እያለ ነው አባቱ ወንደሰን እዚሁ አል-ቶውራ የተባለው ሆስፒታል ውስጥ እያስታመምኩት እጄ ላይ ያረፈው፡፡ አዲስ አበባ ያለው ልጄ እንዳል ግሩም የአባት ፍቅር አጥቶ ማደጉን ሳስበው ሰቀጠጠኝ፡፡ በስደት እኔን በሞት እናቱን ያጣው ልጄ በርቀት ምክንያት የአባትነት ፍቅሬን ልሰጠው እንደማልችል ሳስበው […]
